ናሚቢያ
ከውክፔዲያ
የናሚቢያ ሪፑብሊክ |
||||||
---|---|---|---|---|---|---|
|
||||||
ዋና ከተማ | ዊንድሁክ |
|||||
ብሔራዊ ቋንቋዎች | እንግሊዝኛ፥ አፍሪካንስ | |||||
መንግሥት ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር |
ሂፊከፑኘ ፖሃምባ ናሃስ አንጉላ |
|||||
የመሬት ስፋት አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.) |
825,418 (33ኛ) |
|||||
ገንዘብ | የናሚቢያ ዶላር | |||||
የሰዓት ክልል | UTC +1 | |||||
የስልክ መግቢያ | +264 |
ናሚቢያ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ፣ በስሜን በአንጎላና በዛምቢያ፣ በምስራቅ በቦትስዋና፣ በደቡብም በደቡብ አፍሪቃ ትካለላለች። በ1982 አመተ ምኅረት ነጻነትዋን ከደቡብ አፍሪቃ ስላገኘች በጣም አዲስ አገር ነች። ዋና ከተማዋ ዊንድሁክ ነው።
ታሪክ[ለማስተካከል]
የናሚቢያ በረኅ አውራጃ ከጥንት ጀምሮ በሳን (ቡሽማን)፣ በዳማራና በናማቋ ሕዝቦች ተሰፈረ። በ14ኛው መቶ ዘመን፣ የባንቱ ወገኖች ባስፋፉ ጊዜ አገሩን ሠፈሩ። ክልሉ ግን ከ19ኛው መቶ ዘመን በፊት በአውሮጳውያን አልተዘለቀም። በዚያን ጊዜ ጀርመን ደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ ተብላ አገሪቱ የጀርመን ቅኝ ግዛት ሆነች። ዳሩ ግን ዋልቪስ በይ የተባለው ትንሽ ወደብ ብቻ የእንግሊዝ ግዛት ነበር።
|